Sunday, May 18, 2014

‪ከ አላህ ውጪ እርድ ለማን አይገባው‬!!!


እንደ ቀልድ አንዲት በግ ገዝተህ ማረድህን አትይ ወዳጄ፥ ዝንብ አፍኖ ገድሎ ጀሀነም የተላከ አለና:: እንዲህ ነው ታሪኩ:-
"ሁለት ሰዎች በጣዖት አምላኪዎች ግዛት ያልፉና ሳትገብሩ አትንቀሳቀሱም ይባላሉ:: አንደኛው ግለሰብ እኔ ዘንድ ምንም ነገር የለም ይላቸዋል:: የዚህን ግዜ እንዳው ዝንብ እንኳ ብትሆን ይሉታል:: ሰውዬውም ምን አነታረከኝ ብሎ እፍን ያደርግና ያቀርብላቸዋል፥ መንገድ ተለቀቀለት ማለት ነው - እወቅ! የተለቀቀለት የጀሀነም መንገድ ነው:: 
ሌላኛው ግን በአንጻሩ ከአላህ ውጭ ምንንም ለማንም አካል አልገብርም ቢላቸው አንገቱን ብለው ጀነት ሰደዱት" አሉ መልእክተኛው (ሠለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):: 
አላህ ከእኛ እርድ ዱለቱ ወይ ጥብሱ አይሄድለትም አትድከም፣ ስጋው ቆዳው ቀንዱ ደሙ ፈርሱ እዚሁ አንተ ቤት ቀሪ ነው፥ ባይሆን ይህችን አያህ አንብብልኝ:-

لَن يَنَالَ اللَّهَ لُحُومُهَا وَلَا دِمَاؤُهَا وَلَٰكِن يَنَالُهُ التَّقْوَىٰ مِنكُمْ ۚ كَذَٰلِكَ سَخَّرَهَا لَكُمْ لِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ ۗ وَبَشِّرِ الْمُحْسِنِينَ [٢٢:٣٧
"አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡" (22:37)
እንዴታ! አለሞቼ እራቶቼ አለቆቼ ቁጥቦቹ ታረቁን ባክኾን፥ ይኸው ተቀበሉን ..... ጀባ ብለናል ተብሎ ከታረደ ስጋ ለአላህ የሚደርሰው ክፍሉ የቱ ነው እስቲ ልጠይቅህ? ይሄ ይገርምሀል እንዴ? ትንሽ ቆይቶ እኮ ደግሞ አራጁ በሰላቱ ውስጥ እንዲህ ይል ይሆናል: 
"﴿إِنَّآ أَعْطَيْنَـكَ الْكَوْثَرَ - فَصَلِّ لِرَبِّكَ وَانْحَرْ " 
"ስለዚህ ለጌታህ ስገድ፤ (በስሙ) ሰዋም"::
ልብ ያለው ልብ ይበል!!!

 
 ከ     https://www.facebook.com/firsttewhed  የተወሰደ።

No comments:

Post a Comment