Saturday, December 6, 2014

mewlid 21








የእስልምና መንገድ ማለት ቁርአንን፣ ሱናን፣ የሱሓባዎች ንግግር እና ስራቸውን፣ ኢጅማዕን፣ ቂያስን አጠቃሎ የያዘ ነው።
ቢድዓ መስራት በጣም ትልቅ ወንጀል ነው። ዓሊሞች ወንጀል በክብደቱ መሰረት እንደሚከተለው አስቀምጠዉታል።
-ትልቁ ሽርክ
-ትንሹ ሽርክ
-ቢድዓ
-ትልልቅ ሓራሞች(ዚና፣ ስርቆት፣ ወዘተ )
-ትንንሽ ሓራሞች (አጅነብዪን መጨበጥ፣ ወዘተ )



mewlid 1








بسم الله الرحمن الرحيم

1. 
ነቢዩ መሓመድ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
“ ሁለት ነገሮችን ትቸላችኋለሁ ፣ እነሱን ከያዛቹህ አትጠሙም ፣ እነሱም የአላህ መፅሃፍ (ቁርአን) እና የነቢዩዉ ሱና ናቸው:: ”

Tuesday, November 25, 2014

መውሊድን ማን አከበረው?





بسم الله الرحمن الرحيم

መውሊድን ማን አከበረው?

ነቢዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይህ ወሰለም) -> አላከበሩም


አራቱ የነቢዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይህ ወሰለም) ምትኮች [አቡብከር፣ ዑመር፣ ዑስማን፣ ዓሊይ(ረድየላሁ ዓንሁም)]                    ->አላከበሩም

ሱሓቦች-> አላከበሩም

አራቱ ኢማሞች (ኢማሙ ሻፊዒ፣ ኢማሙ ሓንበሊ፣ ኢማሙ ሓነፊ፣ ኢማሙ ማሊኪ)-> አላከበሩም

ኢማሙ ቡኻሪ፣ ኢማሙ ሙስሊም አላከበሩም

ታብዒዮች -> አላከበሩም

አትባዑ ታብዒዮች -> አላከበሩም

ታድያ ማነው የጀመረው?

የኢስላም እና የነቢዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይህ ወሰለም) ጠላት የሆኑት ራፊዳዎች( ደምበር ያለፉ ሺዓዎች)።


የመውሊድ በዓል በቁርዓንና በሐዲስ መሠረት አለው ብሎ መድከም ከንቱ መሆኑን ማወቅ ይገባል፡፡



የመውሊድ በዓል በቁርዓንና በሐዲስ መሠረት አለው ብሎ መድከም ከንቱ መሆኑን ማወቅ ይገባል፡፡ መውሊድ በነቢዩ የሕይወት ዘመን ፈፅሞ እንዳልነበረ ዑላማዎች ሁሉ ይስማሙበታል፡፡ እንዲያውም መውሊድን የሚያከብሩት ሳይቀሩ ይህንን እውነታ አያስተባብሎም፡፡

ይህ አይነቱ የመልእክተኛዉ ፈለግ የሌለበት ተግባር ደግሞ ወደ አላህ መቃረቢያ መንገድ መሆን እንደማይችል በበርካታ ቁርአናዊና ሀዲሳዊ አስረጆች ተብራርቷል፡፡

በዓሉ መከበር የጀመረዉ ከአራተኛዉ የሒጅራ ክፍለ ዘመን በኋላ ራሳቸዉን “ፋጢሚዬች” ብለው ይጠሩ በነበሩ የኡበይድ አልቀዳህ ዘሮች ነው በግብፅ ነው፡፡


መዉሊድ እንደማይፈቀድ ለማስረዳት ከዚህ የተሻለ ግልጽ አስረጅ የለም። መልካም ተግባር ቢሆን የነብዩ ባልደረቦች ቀድመዉን በተገበሩት ነበር። የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል

‹‹በዚህ በጉዳያችን (በዲናችን) ከእርሱ ያልሆነን ነገር የፈጠረ (ስራው) ተመላሽ ነው፡፡›› አል ቡኻሪይ 2550 እንዲሁም ሙስሊም በቁጥር 1718 ከአዒሻ ዘግበውታል

 ye haji welea sle mewlid daewa lemadamet yihinin link yichanu 





Wednesday, October 22, 2014

አሁንም ቅድሚያ ለተውሂድ!!!



አሁንም ቅድሚያ ለተውሂድ!!!




ድንበር ካለፉ ሱፍያ የጥመት ቡድን አንዱ ስለ ነቅሸበንዲያ ሱፊ ጠሪቃ መሪ ‹‹መውላና ታላቁ ሸይኽ ነዚም ሀቃኒ›› ብለው ስለሚጠሩት የሚከተለውን ኩፍር አባባል ፅፈውለታል

‹‹ (የሱልጣነል አውልያ ደረጃ) የአውልያዎች መሪ (የቁጥብ) ደረጃ››
‹‹የምታየው ነገር ሁሉ በሱልጣነል አውልያ ቁጥጥር ስር ነው፡፡ እዚህ ዩኒቨርስ ላይ ላሉ ሰዎች ሁሉ ሃላፍትናውን የወሰደው እሱ ነው፡፡ የጂኑ አለምም ይሁን የመላኢካዎች አለምንም ጭምር ሃላፍትና ወስዷል፤ የሰው ልጆች መሪ (ሱልጣን) የጂንም የመላኢካም (መሪ) እንደሆነው ሁሉ፡፡
ይህ የሱልጣነል አውሊያ (መቃም) ደረጃ ከልብ ጋር የተገናኘ ደረጃ ነው፡፡ አእምሮ እንኳን የዚህን ደረጃ ትልቅነት አስቦ አይደርስበትም፡፡ ይህ ደረጃ ባለንበት ወቅት ከመውላና ሸይኽ ናዚም ጋር የተቆራኘ ነው፡፡›› ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን


ምንጭ ‹‹ሀቂቀቱል ሀቃኒ›› የተሰኘ የነዚሁ ሱፍዬች አርቲክል

በአላህ ፍቃድ ጥቂት መልሶች
1) የዚህ ዩኒቨርስ አስተናባሪ አላህ ብቻ መሆኑን የድሮዎቹ የቁረይሽ አጋሪያን እንኳን አልከዱም ነበር፡፡ የሚከተለው የአላህ ቃል ለዚህ ማስረጃችን ነው

قُلْ مَن يَرْزُقُكُم مِّنَ ٱلسَّمَآءِ وَٱلْأَرْضِ أَمَّن يَمْلِكُ ٱلسَّمْعَ وَٱلْأَبْصَٰرَ وَمَن يُخْرِجُ ٱلْحَىَّ مِنَ ٱلْمَيِّتِ وَيُخْرِجُ ٱلْمَيِّتَ مِنَ ٱلْحَىِّ وَمَن يُدَبِّرُ ٱلْأَمْرَ ۚ فَسَيَقُولُونَ ٱللَّهُ ۚ فَقُلْ أَفَلَا تَتَّقُونَ

«ከሰማይና ከምድር ሲሳይን የሚሰጣችሁ ማን ነው? መስሚያዎችንና ማያዎችንስ የፈጠረ ማን ነው? ከሙትም ሕያውን የሚያወጣ ከሕያውም ሙትን የሚያወጣስ ማን ነው? ነገሩን ሁሉ የሚያስተናብርስ ማን ነው?» በላቸው፡፡ «በእርግጥም አላህ ነው» ይሉሃል፡፡ «ታዲያ (ለምን ታጋራላችሁ?) አትፈሩትምን?» በላቸው፡፡

ተፍሲር ጠበሪ ላይ የሚከተለውን እናገኛለን
( ومن يدبر الأمر) ، وقل لهم: من يُدبر أمر السماء والأرض وما فيهن ، وأمركم وأمرَ الخلق (50) ؟ ، ( فسيقولون الله) 
ነገሩን ሁሉ የሚያስተናብርስ ማን ነው?
በላቸው በሰማያት፤ በምድርም፤ በመካከላቸው ያለውን ነገር ፤ የናንተንም ጉዳይ ይሁን የፍጡራንን ጉዳይ የሚያስተናብረው ማን ነው በላቸው?
እነሱም (አጋሪዎችም) በእርግጥ አላህ ነው ይሉሃል፡፡

2) አደለም ይህ ወደ ኩፍር የሚጣራ ሰው መላኢካዎች በእርሱ ቁጥጥር ስር ሊውሉ፤ ሊያዛቸው፤ የአደም ልጆች ሁሉ ምርጥ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ጂብሪል (አለይሂ ሰላም) ወህይ ይዞ መምጣት ሲዘገይ እና ሲናፍቃቸው ‹‹ምን ነው እንደ በፊቱ ቶሎ ቶሎ አትመጣም›› ሲሉት የሚከተለውን መልስ ሰጣቸው

وَمَا نَتَنَزَّلُ إِلَّا بِأَمْرِ رَبِّكَ ۖ لَهُۥ مَا بَيْنَ أَيْدِينَا وَمَا خَلْفَنَا وَمَا بَيْنَ ذَٰلِكَ ۚ وَمَا كَانَ رَبُّكَ نَسِيًّا
(ጂብሪል አለ) «በጌታህም ትእዛዝ እንጅ አንወርድም፡፡ በፊታችን ያለው፣ በኋላችንም ያለው በዚህም መካከል ያለው ሁሉ የርሱ ነው፡፡ ጌታህም ረሺ አይደለም፡፡

ስለዚህ ድንበር ያለፉ ሱፍያ የጥመት ቡድን መንገድ የሳተ ሆኖ ሳለ፤ ሱፍያን ጥሩ አድርጎ ለማቅረብ መሞከር ብሎም ‹‹ሱፊያዎች ጭንቀታቸው ሙስሊሙ እንዴት አንድ ሆኖ ንጹህ ቀልብ ይዞ አላህ ፊት ይቀርባል›› ማለት አላህ ፊት የሚያስጠይቅ ነው፡፡ 
ሱፍዬች መንገድ የሳቱ የጥመት ቡድኖች ናቸው፡፡ ስለነሱ የሌላቸውን ባህሪ እየሰጡ እነሱን ጥሩ አድርጎ ማቅረብ አማናን መብላት ነው፡፡ አገራችን ላይ ዛሬ አህባሽ የምንላቸው ትላንት ሱፊ ነን ሲሉ የነበሩ ናቸው፡፡ አንዳንዶች እንዲያውም አንድ ነን ብለው ሁሉ ከተፈራረሙዋቸው መሃል ትላንት ሰፈ ነን ሲሉ ቆይተው ዛሬ አህባሽ የሆኑ አሉ ሸይኽ ጠሃን ይመስል፡፡ ጠሃ ስም ቢቀያይርም ትላንት የነበረውን የሱፊ ኩፍር እምነት ሙታንን መለመን እና የመሳሰሉትን ይዞ ነው አሁንም ያለው፡፡ ሱፍያን አትንኩ፤ አታጋልጡ የሚሉ ሰዎች አላህን ሊፈሩ ይገባቸዋል፡፡

ይህንን ሰው ነዚም ሀቃኒን አገራችን ያሉ አህባሾች ሁሉ ፌስቡክ ላይ ወል ፎቶዋቸው አድርገውት ይንቀሳቀሳሉ፤ የዚህን ሰው ኩፍርያት አሳምረው በማቅረብ ሰው ሊያታሉ ይሞክራሉ፡፡

ባለፈው ካስታወሳችሁ ነዚም ሃቃኒ ‹‹በግራ በኩል ያለው መላኢካ አይፅፍም›› ያለበትን የኩፍር ንግግሩን መልስ የተሰጠበት መሆኑ ይታወሳል፡፡
አላህ ከጠሞ አጥማሚዎች ይጠብቀን፡፡

Tuesday, September 30, 2014

ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ። ክፍል 7


بسم الله الرحمن الرحيم

r الحمد لله رب العالمين، وصلى الله وسلم على رسوله 

በአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ።

ክፍል 7

1.1. ተውሒድ አር-ሩቡብያ

ተውሒር አር-ሩቡብያ ማለት አላህን በስራዎቹ ብቸኛ ማድረግ ነው። አላህን በስራዎቹ ብቸኛ ማድረግ ደግሞ የሚከተሉትን ነጥቦች አውቆ(ተረድቶ) በነሱ ማመንን ያጠቃላል። 
ሁሉንም አለማት የፈጠረው አንድ አላህ ነው።
ሲሳይ ሰጪ አንድ አላህ ነው።
ሂያው አድራጊ፣ ከህያው ነገርም ሙታንን የሚያወጣ አንድ አላህ ብቻ ነው።
ሂደቶች ሁሉ እንዲከሰቱ የሚያደርገው አንድ አላህ ብቻ ነው።

Wednesday, August 27, 2014

ፈጣሪ ቀላቢ፤ ፍጡራን ተቀላቢ፡፡




ፈጣሪ ቀላቢ፤
ፍጡራን ተቀላቢ፡፡

ፍጥረተ አለሙን የፈጠረ፤ የሚያስተናብር፤ የሚቀልብ አላህ ብቻ ነው፡፡ ይህንን ከአላህ ውጭ ያለ ያደርገዋል ብሎ መናገርም ይሁን ማመን ክህደት ነው፡፡ ሁሉን የፈጠረ ቀላቢ፤ ሁሉም ፍጡራ የብቸኛው ፈጣሪ ተቀላቢ ሆነው ሲያበቁ፤ ጥራቻ ለአላህ የተገባው ይሁን አገራችን ላይ የሚከተሉትን ክህደት እና ባዕድ አምልኮዎች እናገኛለን፡፡


1) አላሁመሰሊ አላ ሙሀመዲ
መገን ነቢ (በጣም ይገርማሉ ነቢ)
የሁሉ ቀላቢ

2) ለካም አንቱ ነሁ ያነቢ
ለመላው ኸልቅ ቀላቢ
ብትን ያለውን ሰብሳቢ
በሶፋ ቡራቅ ጋላቢ

3) አባድር ፆም አያሳድር፡፡

እነዚህ ከላይ ያነበባችኋቸው የክህደት፤ የኩፍር ቃላት ናቸው፡፡ አላህ ስለ እራሱ እንዲህ ሲል ይናገራል፡፡
وَمَا مِن دَآبَّةٍ فِى ٱلْأَرْضِ إِلَّا عَلَى ٱللَّهِ رِزْقُهَا وَيَعْلَمُ مُسْتَقَرَّهَا وَمُسْتَوْدَعَهَا ٰ 
በምድርም ላይ ምንም ተንቀሳቃሽ የለችም ምግቧ በአላህ ላይ ያለ ቢኾን እንጂ፡፡ ማረፊያዋንም መርጊያዋንም ያውቃል፡፡ 
إِنَّ ٱلَّذِينَ تَعْبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ لَا يَمْلِكُونَ لَكُمْ رِزْقًا فَٱبْتَغُوا۟ عِندَ ٱللَّهِ ٱلرِّزْقَ وَٱعْبُدُوهُ وَٱشْكُرُوا۟ لَهُۥٓ ۖ إِلَيْهِ تُرْجَعُونَ
ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፡፡ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትግገዙዋቸው (መላኢካዎችም፤ ነብያትም (ኢሳን፤ ኡዘይርን፤ ነብዩ ሙሃመድን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፤ ደጋጎችም አልይም፤ ሁሴንም፤ ፋጢማም፤ ጠንቋይም፤ ጂንም እናም ሌሎችም) ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፡፡ ስለዚህ ሲሳይን ከአላህ ዘንድ ብቻ (ፍጡራኑን የሚያብቃቃ ፍጡራኑን የሚያብቃቃ ብቸኛው አምላክ፤ ብቸኛው ፈጣሪ አላህ ከእርሱ ብቻ) ፈልጉ፡፡ ተገዙትም (ለእርሱ ብቻ የሚገቡትን መብቶች ለፍጡን አሳልፋችሁ አትስጡ)፡፡ ለእርሱም አመሰግኑ፡፡ ወደእርሱ ትመለሳላችሁ፡፡

ተውሂድ ማለት አላህ ብቻ የሚነጠልበትን መነጠል ሲሆን፡፡ ሽርክ ደግሞ ለአላህ ብቻ የሚገቡትን ወይንም አላህ ብቻ የሚነጠልባቸውን ከእርሱ ውጭ ላለ ማንም አካል (ፍጡር ማለት ነው፡፡ ብቸኛው ፈጣሪ እሱ ብቻ ሆኖ ሳለ) ይሁን አሳልፎ ለፍጡራን መስጠት ነው፡፡

በአላህ ላይ ማጋራት ከባድ ወንጀል እና በደል ነው፡፡ እያጋራ የሞተ ሰው መኖርያው እሳት ነው፤ ጀነት በእርሱ ላይ እርም ናት፡፡ የአላህ ባርያዎች ሆይ! የሽርክን አስከፊነት ተገንዝበን እራሳችንን፤ ቤተሰባችንን፤ ዘመዶቻችንን፤ መላውን ማህበረሰብ ከእሳት በአላህ ፈቃድ ልናድን ይገባናል፡፡

የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያ፤ በቤተሰቦቻቸው፤ በባልደረቦቻቸው፤ ሃቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡

Monday, August 25, 2014

Amharic arbeen

https://play.google.com/store/apps/details?id=appinventor.ai_abuadnanabumeriem.ArbeenAnewewiyah

Tuesday, August 19, 2014

አላህን ከአምሳያና ከጉድለት ማጥራት ‘ተንዚህ’ በአህሉሱና እና በአህባሾች እይታ






አላህን ከአምሳያና ከጉድለት ማጥራት ‘ተንዚህ’ በአህሉሱና እና በአህባሾች እይታ

አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ Salah Ahmed (ሃፊዘሁላህ)
══════════════════════
www.nesiha.org {{ መነበብ ያለበት }}
══════════════════════
አህሉሱና የአላህን ባህሪያት ከአምሳያና ከጉድለት ማጥራት “ተንዚህ”ን በተመለከተ ያላቸው አቋም በሁለት መሰረቶች ላይ የተገነባ ነው።

አላህን ከአምሳያ ማጥራት (ነፍዩል ሙማሰላህ)፡- አላህን ከፍጥረታት ምንም ነገር በምንም አይነት ባህሪ አይመስለውም፤ አላህም ከፍጥረታቱ ምንንም አይመስልም።

አላህን ከጉድለት ማጥራት (ነፍዩ-ነቃኢስ)፡- አላህ ጉድለትን ከሚያመላክቱ ባህሪያት ሁሉ የጠራ ነው። ማንገላጀት፣ እንቅልፍ፣ አቅም ማጣት እና አለማወቅን ከመሳሰሉ የጉድለት ባህሪዎች ሁሉ የጠራ ነው።

ይሁንና፤ አብዛኛዉን ጊዜ በቁርአን ላይ ‘አላህን ከጉድለትና ከመመሳሰል ማጥራት’ ጥቅል በሆነ መልኩ የሚቀርብ ሲሆን፤ የአላህን ባህሪያት ማጽደቅ ግን በዝርዝር ሲቀርብ እናገኛለን። ተከታዮቹ አንቀጽ ይህንን መርሆ በጉልህ ያሳያል፤

)لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ ( الشورى: ١١

‹‹የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡» (አል ሹራ 11)

ይህ አንቀፅ የሚያስረዳው በየትኛውም ሁኔታ በፍጡራንና በፈጣሪ መካከል መመሳሰል እንደሌለና አላህ ሰሚና ተመልካች መሆኑን ነው፡፡ መስሚያና መመልከቻ የብዙ ፍጡራን መገለጫዎች ቢሆኑም ነገር ግን የአላህ መስሚያና መመልከቻ ከፍጡራኑ ጋር አይመሳሰልም፡፡ በመስሚያና በመመልከቻ አምሳያ እንዳሌለው ሁሉ በሌሎችም ባህሪያቱ አምሳያ የለውም፡፡

አንቀጹ የጉድለት ባህሪዎችን ጥቅል በሆነ መልኩ ዉድቅ ሲያደርግ ምሉዕ ባህሪዎችን ግን በዝርዝር ያጸድቃል። ይህ አንቀጽ ሙስሊሞች ለአላህ የማይገቡ ባህሪያትን ከመረዳት አንጻር ሊኖራቸው ለሚገባው ትክክለኛ አካሄድ መርሆን ይቀርጻል። ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው ሌሎች አንቀጾችም ይገኛሉ።

==> አላህ እንዲህ ብላል፦

)فَلَا تَضْرِبُوا لِلَّهِ الْأَمْثَالَ إِنَّ اللَّهَ يَعْلَمُ وَأَنْتُمْ لَا تَعْلَمُونَ ( النحل: ٧٤

“ለአላህም አምሳያዎችን አታድርጉ አላህ ያውቃል፤ እናንተ ግን አታውቁም፡፡” (አል ነህል 73)

አል ኢማም አጦበሪይ ይህን አንቀፅ በማብራራት እንዲህ ብለዋል፤

" فلا تمثلوا لله الأمثال ولا تشبهوا له الأشباه فإنه لا مثل له ولا شبه "

“አምሳያም ቢጤም የለውምና ለአላህ አምሳያና ቢጤ አታድርጉ” ተፍሲሩ ጦበሪ 7/621

==> አላህ እንዲህ ብላል፦

(وَلَمْ يَكُنْ لَهُ كُفُوًا أَحَدٌ) الإخلاص: ٤

«ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም» (አል ኢኽላስ 4)

ታላቁ የቁርአን ተንታኝ አል ኢማም አጦበሪይ እንዲህ ብለዋል:

" ولم يكن له شبيه ولا عدل وليس كمثله شيء "

‹‹አምሳያም አቻም የለውም እንደ እርሱ አምሳያ ምንም የለም፡፡››

==> አላህ እንዲህ ብላል፦

(هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا) مريم: ٦٥

«ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን» (መርየም 65)

ኢብኑ ዓባስ ይህን አንቀፅ ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ:

" هل تعلم للرب مثلًا أو شبيهًا "

“ለአላህ አምሳያ ወይም ቢጤን ታውቃለህን?”

አህሉሱና የአላህን ባህሪዎችን ሲቀበሉና ሲያጸድቁ ከፍጡራን ባህሪዎች ጋር ምንም እንደማይመሳሰሉ ቀድመው ያምናሉ። ከላይ በተመለከተው ቁርአናዊ አካሄድ መሰረት ለአላህ ባህሪያትን በዝርዝር ማጽደቅና ጉድለትና መመሳሰልን በጥቅሉ ውድቅ ማድረግ አህሉሱና ከጥንት ጀምሮ የተጓዙበት አቅጣጫ ነው። እንደ አህባሾች በዚህ ፍጥረተ ዓለም ዉስጥ የሚገኙ ፍጥረታትን እና ባህሪዎቻቸውን በዝርዝር በማውሳት “አላህ ሰማይንና ምድርን አይመስልም፣ ጸሀይንና ጨረቃንም አይመስልም፣ ሰዉንና መላኢካን አይመስልም… ወዘተ” በማለት ዝርዝር የማነጻጸር አካሄድን አይከተሉም። በእርግጥ ለተለያዩ ምክኒያቶች በቁርአንና በሀዲስ ለአላህ እንደማይገቡ የተነገሩና በዝርዝር ውድቅ የተደረጉ አንዳንድ ባህሪዎችን እናገኛለን። በቅድሚያ ጥቂቶቹን እንመልከት እና መረጃዎቹ ምን እንደሚያመላከቱ እንገልጻለን። መመሳሰልን እና የጉድለት ባህሪዎችን በዝርዝር ዉድቅ በማድረግ ለአላህ የተገቡ ምሉእ ባህሪዎችን ከሚያጸድቁ ቁርዓናዊና ሀዲሳዊ መረጃዎች መካከል፤

قوله تعالى: )وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لا يَمُوتُ (الفرقان: 58

«በዚያም በማይሞተው ‘ሕያው’ አምላክ ላይ ተመካ፡፡» አልፉርቃን 58

قوله تعالى: )اللَّهُ لا إِلَهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ لا تَأْخُذُهُ سِنَةٌ وَلا نَوْمٌ ( البقرة : 255

«አላህ ከእርሱ በቀር በሀቅ የሚመለክ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ራሱን ቻይ ነው፡፡ ማንገላጀትም እንቅልፍም አትይዘውም፡፡» አልበቀራህ 255

لما رفع بعض الصحابة أصواتهم بالتكبير وهم معه في السّفر قال رسول الله ه: "أيها الناس ارْبعُوا عَلَى أَنْفُسِكُمْ فَإِنَّكُمْ مَا تَدْعُونَ أَصَمَّ وَلَا غَائِبًا إِنَّمَا تَدْعُونَ سَمِيعًا بَصِيرًا ..." رواه البخاري ومسلم

የአላህ መልዕክተኛ ه በጉዞ ላይ እያሉ አንዳንድ ባልደረቦቻቸው ድምጻቸውን በጣም ከፍ አድርገው ተክቢር ሲያደርጉ እንዲህ ብለዋቸዋል፦ «እናንተ ሰዎች ሆይ! ለነፍሳችሁ እዘኑላት፤ እናንተ የምትጣሩት የማይሰማን አምላክ አይደለም፤ እሩቅም አይደለም። የምትጣሩት፤ ሰሚና ተመልካች የሆነውን አምላክ ነው።» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል

እነዚህ እና መሰል አንቀጾች፤ ከላይ የተመለከተዉን “በጥቅል ዉድቅ የማድረግ እና በዝርዝር የማጽደቅ” ቁርአናዊ አካሄድና መርሆ የሚጻረሩ አይደሉም። ምክኒያቱም፤ እነዚህን የጉድለት ባህሪዎች በዝርዝር ውድቅ የማድረግ አላማ የእነርሱን ተቃራኒ ምሉዕ ባህሪያት ለአላህ ማጽደቅ ነው። ለምሳሌ፤ አላህ እንቅልፍ እና ማንገላጀት እንደማይዘው መግለጹ፤ በውስጡ ያዘለው፤ የተሟላ ህያዉነት “ሀያት” እና ነገሮችን ሁሉ ማስተናበር “ቀዩሚያህ” አላህ የሚገለጽባቸው ባህሪያት መሆናቸውን ነው። አንድን ባህሪ ዉድቅ ስናደርግ የዚያን ባህሪ ተቃራኒ በተሟላ መልኩ ለአላህ እናጸድቃለን። አህሉሱና ዘንድ፤ ዉድቅ የሚደረጉ ባህሪዎች ሁሉ በተቀራኒ ምሉእነትን የሚያመላክቱና መልካም ባህሪዎችን ባማረ መልኩ የሚያጸድቁ መረጃዎች ናቸው። ስለዚህ፤ እነዚህ በዝርዝር ዉድቅ የተደረጉ የጉድለት ባህሪያት በተዘዋዋሪ መልካም ባህሪያትን በዝርዝር የማጽደቅ አካል ናቸው። በቁርአን እና በሀዲስ ውድቅ የተደረጉ የጉድለት ባህሪዎችን በተመለከተ ትክክለኛው የአህሉሱናም አቋም ይኸው ነው።

ስለዚህ፤ በቁርአን ላይ ወጥነት ባለው መልኩ ተቀርጾልን የምናገኘው አካሄድ እና መርሆ “አላህን ከአምሳያና ከጉድለት በጥቅሉ ማጥራት እና የአላህን ባህሪያት በዝርዝር ማጽደቅ” ነው።

የጃሂሊያ ሰዎች፤ “መላዕክት የአላህ ልጆች ናቸው” ሲሉ፤ አላህ ይህ አይነቱ ባህሪ ለእርሱ እንደማይገባው ገልጿል፤ በአየቱል ኩርሲይም ህያውነቱን በመግለጽ እንቅልፍ እና ማንገላጀት እንደማይዘው ገልጿል፤ ሰማያትና ምድርን በመፍጠሩ ድካም እንዳልነካው ተናግሯል። አህሉሱና ይህንን ተቀብለው ለአላህ እንደማይገቡ በማረጋገጥ እና በተቃራኒው ምሉእ የሆኑ መልካም ባህሪዎችን በማጽደቅ ብቻ ይቆጠባሉ። ልጅ እንደሌለው ስለተገለጸ፤ አባትም የለዉም፣ እናት የለዉም፣ ወንድም የለዉም...ወዘተ የሚል አካሄድ የላቸውም። አህባሾች ግን ለመስማት በሚቀፍ አገላለጽ ብዙ ፍጥረታትን እና ባህሪዎቻቸዉን በመደርደር “አላህ ይህንን አይመስልም ያንንም አይመስልም” ይላሉ። ለምሳሌ፤ አላህ መላእክትን አይመስልም፣ ጂንንም አይመስልም፣ሰው አይመስልም፣ አካል አይመስልም፣ ብርሀንን፣ድንጋይን፣ ዛፍን አይመስልም…ወዘተ በማለት ደጋግመው መናገራቸው የተለመደ ነው። ሸይኻቸው አብዱላህ አልሀረሪ “አሸርሁል ቀዊም” በሚለው መጽሀፉ ገጽ 107 / “አሲራጡልሙስተቂም ገጽ 28 እና በብዙ ጽሁፎቹ ይህን አይነት ዝርዝር አስቀምጧል። “አልዓቂደቱል ኢስላሚያህ” በሚል ርዕስ ባቀረበው ሙሀደራ እንዲህ ብሎ ነበር፤« በቁርአን እንደመጣው፤

(ليس كَمِثْلِهِ شَيْءٌ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِير) الشورى: ١١

‹‹የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡» (አል ሹራ 11)

የአንቀጹ ትርጉም፤ አላህን ከፍጥረታት ምንም የሚመስለው የለም፣ከባድ አካልም ይሁን ቀላል አካል አይመስለዉም፣አላህ ሰውን አይመስልም፣መላእክትንም፣ መንፈስንም፣አይመስልም፣ብርሀንንም ይሁን ጨለማን አይመስልም፣ ተጨባጭ ከሆኑ ግዑዝ አካላትም እንደ ድንጋይ እና ዛፍንም አይመስልም»

ይህ አካሄድ ከላይ ለመመልከት የሞከርነዉን ቁርአናዊ አካሄድ የሚጻረር የጥመት መንገድ መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም። ውድ አንባቢ፤ አንድ ሰው ሊያወድስህ እና ሊያሞካሽህ አስቦ፤ “አንተ እኮ ሌባ አይደለህም፣ ማጅራት መቺ ቀማኛም አይደለህም” ቢልህ ደስታን ይፈጥርልሀልን? በእርግጠኝነት መልስህ የሚሆነው “እንዲህ አይነቱ ሰው ተገቢዉን ክብር አልሰጠኝም የሚል ነው”። ሀቅን ከመረዳት ቢድዓና ፍልስፍናዎች አይምሮዉን ለበረዙት ሰው ካልሆነ በቀር ይህ ግልጽ ነገር ነው። የሰይፍን ስለታማነት ለማድነቅ ከዱላ ጋር ያነጻጸረ በተቃራኒው ዱልዱምነቱን እየገለጸ ለመሆኑ አያጠራጥርም። አላህ ከጥፋት እና ከመደናበር ይጠብቀን። ምስጋና ለሀያሉ አላህ የተገባ ነው።

--------------------------------------
--------------------------------------

የተወሰደ።


Tuesday, August 5, 2014

ኡሱሉ ሰላሳ ኦድዬ ፋይል ክፍል 6






ኡሱሉ ሰላሳ
ኦድዬ ፋይል 
ክፍል 6
4.29 MB ከሚከተሉት ሊንክ ዳውንሎድ አድርጉ


Wednesday, July 30, 2014

ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ። ክፍል 6


بسم الله الرحمن الرحيم

r الحمد لله رب العالمين، وصلى الله وسلم على رسوله


በአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ

ክፍል 6
 1.  በአላህ ማመን።
በአላህ ማመን ሶስት ነገሮችን ጠቅሎ ይይዛል።
1.1.  ተውሒድ አር-ሩቡብያ
1.2.  ተውሒድ አል-ኡሉሁያ

1.3.  ተውሒድ አል-አስማኡ  ወ አሲፋት

Friday, July 25, 2014

አላህ ከሰማይ በላይ፣ ከዓርሽ በላይ ለመሆኑ ማስረጃዎች። ክፍል 1




بسم الله الرحمن الرحيم
وصلى الله وسلم على رسوله (صلى الله عليه و سلم)
 الحمد لله رب العالمين،
በአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

ላህ ከሰማይ በላይ፣ ከዓርሽ በላይ ለመሆኑ ማስረጃዎች።
ክፍል 1

 إِذْ قَالَ ٱللَّـهُ يَـٰعِيسَىٰٓ إِنِّى مُتَوَفِّيكَ وَرَافِعُكَ إِلَىَّ  
55  آل عمران

 
አላህም ባለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ ዒሳ ሆይ! እኔ ወሳጂህ ወደ እኔም አንሺህ ነኝ፡፡
 [3:55] 

Friday, July 18, 2014

አብሬት


በየ ዓመት ረጀብ 15 ይከበራል ። ምንም ታስቦ ይመስረት በኢስላም መነፅር ሲታይ ክብረ በዓሉ ቢድዓ ነው ነብዩ ያልሰሩት አዲስ ፈጠራ ። አዒሻ ባስተላለፈችውና ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል " የኛ ትዕዛዝ የሌለበት የትኛውም አይነት ስራ የሰራ ስራው ተመላሽ ነው ።" ፈጠራ ደግሞ ጥመት ነው የጥመት መጨረሻው እሳት ነው የአላህ መልክተኛ እንዳስጠነቀቁት 
በአጭር የዚህ ቢድዓዊ ክብረ በዓል ውጤቱ ይህን ይመስላል ። ከፈጠራነቱ በሻገር ይህ ነው የማይባል ተቆጥሮ የማይዘለቅ የሽርክ አይነት ይሰራል። የአላህ ሀቅ ለፍጡር ይሰጣል ። በተለያዩ አቅጣጫዎች በሬና ምኩት እየተነዳ ስለታቸውን ለመሙላት መሰዋት ያቀርባሉ ፤ ከመቃብሩ ዙርያ በማጎብደድ ስሮንደ (ድረሱልን) እያሉ ይማፀናሉ ፤ ያገኛቸውን ችግር አንድ በአንድ በዝርዝር ያቀርባሉ ሰምተው ምላሽ መስጠት ባይችሉም እንኳ ። የተለያዩ የውዳሴ ዜማዎችንም በግሩፕ ያዜማሉ ፤ ዘላለማዊ ህይወት የተሰጠው ባይኖርም ዘላለማዊ ሕይወትን ለሸይኹ ይመኛሉ

" አበራሙዝ ሸሊላህ ሰንብቶኒ
አበራሙዝ ሸሊላህ ደውሞኒ "

እየከመሩ የሚያስቀምጡት ነገር ውጤቱ መራራ መሆኑን ባያውቁም እንዲህ በማለት ያንጎረጉራሉ

" አብሬት ጀፎረ ቲኮሬ 
የጀነት ሸረት ይወሬ "

አብሬት መንደሩ ላይ የጀነት ምግብ ይበላል እነደማለት

ኢስቲጋሳ ይደረግባቸዋል በመንዙማ መልክ

"አጊስና ሰይዲ የአበል ኩመላ
ሚፍታሁ ሊልኸይሪ ሂጃቡ ሊልበላ "

አላህ ግን ከሱ ውጭ ያሉ ነገሮች በአጠቃላይ መድረስና መርዳት እንደማይችሉ በምሳሌ እንዲህ እያለ ያስረዳል

يأيها الناس ضرب مثل فاستمعوا له إن الذين تدعون من دون الله لن يخلقوا ذبابا ولو اجتمعوا له وإن يسلبهم الذباب شيئا لا يستنقذوه منه ضعف الطالب والمطلوب 

الحج 73 

እናንተ ሰዎች ሆይ ምሳሌ ተደርጎላችዋልና አዳምጡ እነዚያ ከአላህ ውጭ የምትጠሯቸው ነገሮች ዝንብ እንኳ መፍጠር አይችሉም ቢሰባሰቡም እንኳ (ተጋግዞ ለመፍጠር) (ከምግባቸው ላይ) ዝንብ አንዳች ነገር አንስቶባቸው ቢሄድ ማስጣል አይችሉም ፈላጊውም ተፈላጊውም ደካማ ተደረገ

የዚህ ከንቱ ልፋት መጨረሻው ምን ይሁን ? እውን እነሱ እንደሚሉት የአብሬት ሸይኽ በሕይወት ኑረው ጥሪውን ሰምተው ምላሽ ይሰጣሉ ወይስ የሉም?

መ) ያለምንም ጥርጥር በሕይወት የሉም የአካባቢው ተወላጅ ( ሙሪዱ) ሲሞቱ ባያይም አላህ ደግሞ ዘለዓለማዊ ሕይወት ለማንም አልሰጠምና የሉም ብለን እንደመድማለን ።

"ካንተ በፊት ለማንም ዘላለማዊ ሕይወት አልሰጠንም አንተ ብትሞት አነሱ ዘውታሪ ይመስሉሃልን? " አል አንቢያእ 34
አስከትሎም አንቀጽ 35 ላይ ሁሉም ነፍስ ሞት ቀማሽ መሆኗን ይናገራል ።
አይ መኖር የሉም ካሉበት ሆነው ምላሽ ይሰጣሉ የሚል ካለ አላህ እንዲህ ይላል 

والذين تدعون من دونه ما يملكون من قطمير إن تدعوهم لا يسمعون دعاءكم ولو سمعوا مااستجاب لكم ويوم القيامة يكفرون بشرككم ولا ينبئك مثل خبير 

فاطر 13-14 

እነዚያ ከአላህ ውጭ የምትጠሯቸው ነገሮች የቴምር ከፈፍ ቢሆንም እነኳ አይቆጣጠሩም ፤ ብትጠሯቸው ጥሪያችሁ አይሰሙም ፤ እንደው ቢሰሙ እንኳ አይመልሱላችሁም ፤ በትንሳዔው ቀን ስታጋሩት በነበረው ነገር ይክዳሉ ፤ ይህን የመሰለ ዜና የሚነግርህ ማንም የለም 

አላህ የአብሬት ሸይኽ እና መሰል የሚመለኩ አካላቶች ወደ ራሳቸው አምልኮ ተጣርተው ቢሆንም ባይሆንም በቂያማ ቀን ይጠይቃቸዋል ። ሆኖም 
እነዚህ አካላቶች ተገዙኝ ያላሉ እንደሆነ ተከታዮች ያላቸው እጣ ፈንታ ይህ ነው አላህ እንደሚነግረን

" እነዚያ በአላህ ላይ ሲያጋሩ የነበሩ ቢያዩ ኖሮ ( በቂያማ ቀን የሚሆኑት ነገር ) ፦
የአላህ ቅጣት ባዩ ጊዜ ፣ ኃይል ( ስልጣን ) በአጠቃላይ የአላህ መሆኑን እና ለአላህ እጅግ የበረታ ቅጣት እንዳለው ባዩ ጊዜ ፤ አስከታዮች (በአላህና ላይ የሚጋሩት ) ከተከታዮቻቸው (ከአጋሪዎች) ሽርክ በጠሩ ጊዜ ፣ ቅጣትንም ባዩ ጊዜ መንገዶች (በአጋሪና በተጋሪው መዳረሻ) በተቋረጡ ጊዜ ፤ ተከታይ የነበሩ ሰዎች ይላሉ " ለኛም ወደ ዱንያ የመመለስ እድል ቢኖረን ኖሮ እነኚህ ከኛ እንደጠሩት እኛም ከነሱ እንጠራ ነበር ።" ልክ እንደዚሁ የከሰሩ ሲሆኑ ሥራቸው (አላህ) ያሳያቸዋል እነሱም ከእሳት የሚወጡ አይደሉም "
አል በቀራህ 165–167 

ስናጠቃልል
*********

* እኔ የምሄድው ለኢባዳ እንጂ ምንም ፈልጌ አይደለም የሚል አይጠፋም

መ) የአላህ መልክተኛ " ኮርቻ ወደ ሦስት ቦታዎች እንጂ አይጫንም ወደ አላህ ቤት ፣ ወደ መስጂድ አቅሷ እኔ ወደ መስጂዴ (መዲና) "

እኛም ደግሞ ስንቅ ሰንቆ መኪና ነድቶ ወደ ቀብር ቢድዓ እና ሽርክ ለመስራት አይኬድም እንላለን ሀዲሱ መረጃ በማድረግ

* የሚያጋጥመንን በዝርዝር በማስቀመጥ እንደምንቆጭ ተቆጭተን እንኳ ዳግም የመመለስ እድል እንደሌለን አላህ አበክሮ ነግሮናልና የቂያማ ቀን ጸፀት የሚያከናንበን አንስራ 

* አብዛኞቹ ባለ ማወቅ ይሰራሉ ብለን ባናከፍራቸውም እንኳ ተግባሩ የኩፍር ነውና ጥንቃቄ እናድርግ

* አሻራኪ ምንም ያህል መልካም የሚያስበው ስራ ቢኖ የተፀፀተ ሲሆን ጀሀነም ውስጥ ዘውታሪ ነው ።

በመጨረሻም
።።።።።።።።

አብሬት የሚተገበረው ሽርክ በአጭሩ ፎቶግራፉ ላይ የተመለከተው ይመስላል
ሁለት አድሪሀዎች የባልና የሚስት ሰዎች በዙርያቸው ይጠውፋሉ ፣ በግንባራቸው ይደፋሉ ፣ አፈሩን ይቅማሉ ፣ በጀመዓ ብዙ ረከዓ ይሰግዳሉ… ወዘተ ።
አላህ ትርፍ ከሌለው ስራ ይጠብቀን አሚን

Tuesday, July 8, 2014

ኡሱሉ ሰላሳ ኦድዬ ፋይል ክፍል 5



ኡሱሉ ሰላሳ

ኦድዬ ፋይል 
ክፍል 5

4.47 MB ከሚከተሉት ሊንክ ዳውንሎድ አድርጉ


Saturday, June 28, 2014

ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ። ክፍል 5



بسم الله الرحمن الرحيم
r الحمد لله رب العالمين، وصلى الله وسلم على رسوله


በአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ
 ክፍል 5
 የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረት) ማእዘናት የሚከተሉት ናቸው።
በአላህ ማመን።
በመላኢኮች ማመን።
በመጻህፍት ማመን።
በመልእክተኞች ማመን።
በመጨረሻው ቀን ማመን።
በቀደር ማመን።
  እነዚህ የተጠቀሱት የእስልምና ዓቂዳ ማእዘናት ለመሆናቸው ከቁርአንና ከሓዲስ ብዙ ማስረጃዎች አሉ።

Thursday, June 26, 2014

አዛኙ ጌታ(አላህ) ከዓርሽ በላይ ነው።



- ﺑﺴﻢ اﻟﻠﻪ اﻟﺮﺣﻤﻦ اﻟﺮﺣﻴﻢ -
በአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እና አዛኝ በሆነው።



(الرَّحْمَٰنُ عَلَى الْعَرْشِ اسْتَوَىٰ)
[سورة طه : 5]

አዛኙ ጌታ(አላህ) ከዓርሽ በላይ ነው።


Allah is above the throne.


Saturday, June 21, 2014

ኡሱሉ ሰላሳ ኦድዬ ፋይል ክፍል 4


ኡሱሉ ሰላሳ

ኦድዬ ፋይል 

ክፍል 4

3.28 MB ከሚከተለው ሊንክ ዳውንሎድ አድርጉ

Thursday, June 19, 2014

ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ። ክፍል 4



بسم الله الرحمن الرحيم
الحمد لله رب العالمين، وصلى الله وسلم على رسوله


በአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

ተከታታይ የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ።  


ክፍል 4

የእስልምና ዓቂዳ ማለት ምን ማለት ነው?

የእስልምና ዓቂዳ ማለት የእስልምና ሃይማኖት መሰረት የሆኑ እምነቶችን እና ተግባሮችን ጠቅሎ የያዘ ነው። የእስልምና ዓቂዳ እስልምናን ከሌሎች ሃይማኖቶች በዋነኝነት የሚለየው ነው። አንድ ሰው ባለው ዓቂዳ መሰረት ሙስሊም(የእስልምናን ዓቂዳ ከያዘ) ወይንም ከሃዲ(የከሃድያንን ዓቂዳ ከያዘ) ይሆናል ።

Tuesday, June 17, 2014

አልከሶ



አልከሶ ለመሄድ ከተሰናዳክ አሊያም ቤተሰቦችክን ገንዘብ ሰጥተክ ወደዚህ ቦታ ለመሸኘት ከተነሳክ ለማንኛውም ቦታው ላይ አላህ ያወገዛቸው ምን ምን ነገራቶች እንደሚከናወኑ ፍንጭ ልስጥክ አድምጠኝ!!


ግጭት ቁ.1 ዘምዘም ውሃ የሚገኘው በመካ ከተማ በተከበረው አላህ ቤት አቅራቢያ እንጂ ስልጤ ክልል አይደለም ፤ በረካም የሚፈለገው ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለም
(( ኑሕ ሆይ ከኛ በሆነ ሰላም ባንተ ላይና አንተም ጋር ባሉት ሕዝቦች (ትውልድ) ላይ በሆኑ በረከቶችም የተጎናጸፍክ ሆነህ ውረድ)) ሁድ #48



ዕርዳታ የሚጠየቀው ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለም
ዘወትር በቀን በትንሹ አስራሰባት ጊዜ ፋቲሃ ላይ የምንለው ለዚህ መልስ ነው
(( አንተን ብቻ እንገዛለን አንተን ብቻ ዕርዳታ እነጠይቃለን)) ፋቲሐህ #5



በረካ የሚሰጠው አላህ እንጂ የቀብር አፈር አይደለም
(( (ኢሳም አለ) በየትም ስፍራ ብኾን ብሩክ አድርጎኛል)) መርየም ‪#‎ሰላሳ‬ አንድ



ጉዳይን የሚያስፈፅመው ችግር እንዲያስወግድልን ዕርዳታ የሚጠየቀው አላህ ብቻ ነው
((ወይም ያ ችግረኛን በለመነው ጊዜ የሚቀበል መከራንም የሚያስወግድ በምድርም ላይ ምትኮች የሚያደርጋችሁ፤ (ይበልጣልን? ወይስ የሚያጋሩት?) ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን? ጥቂትንም አትገሠጹም። )) አል፡ነምል ስድሳ ሁለት



ወደሳቸው_ቀርቦ_ልክ_ስጁድ_ያህል_በማጎንበስ_እጃቸውን_ለአፍታ_ስሞ_መውጣት
ስለት የሚገባውም ዕርዳታ የሚጠየቀውም ሱጁድ የሚገበደድለትም አላህ ብቻ ነው
«ስግደቴ፣ መገዛቴም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው» በል፡፡ አንዓም#162


(( ረሱል ሰላላሁአለይሂወሰለም « ከከሃዲዎች ጋር የተመሳሰለ ከነርሱ ነው» ))


ዝናብ የሚለመነው አንድ አላህ ብቻ ነው ዕርድም የሚገባው እርሱ ብቻ ነው
(( ስለዚህ ለጌታህ ስገድ፤ (እርድ) ሠዋም (ለርሱ ብቻ) )) ከውሠር #2


ድረስልኝ የምንለው አላህን ብቻ ነው
((ብትጠሩዋቸው ጥሪያችሁን አይሰሙም፤ ቢሰሙም ኖሮ ለናንተ አይመልሱላችሁም)) ፈጢር #14


(( ረሱል ሰላላሁአለይሂወሰለም «ከአላህ ውጪ ባለ ፍጡር የማለ በርግጥ አጋርቷል»))


(( የዒምራን ባለቤት (ሐና) «ጌታዬ ሆይ፦ እኔ በሆዴ ውስጥ ያለውን (ፅንስ ከሥራ) ነጻ የተደረገ ሲኾን ለአንተ ተሳልኩ፡፡ ከእኔም ተቀበል አንተ ሰሚው ዐዋቂው ነህና»ጊዜ (አስታውስ) )) ዒምራን #35
____


አላህ ቤተሰቦችክን በጀነት እንዲያኖራቸው ከፈለግክ ከዚህ ስፍራ መሄድን እንዲቆጠቡ አሁኑኑ አድርግ (አልረፈደም)
ይሄን መረጃ አልከሶ ቦታው ድረስ በመሄድ ዱዓቶችንና ከዚህ (ከ አልከሶ) በተሰብ ወደ ሱና የተመለሱ ሰዎችን ጠይቆ መረጃ ያቀበለኝን ወንድሜ ኡመር ኢብኑ ኡመር አላህ እጥፍ ድርብ ምንዳ ይሸልምልኝ ::
___________

አላህ ቤተሰቦቻችንን ወደ ተውሂድ ይምራልን ፤ ባለማወቅ የሚያደርጉትንም ሂዳያ ይስጣቸው ፤ ለሽርክና ቢድዓ ጥብቅና የሚቆሙትን አላህ ሂዳያ ይስጣቸው