Tuesday, October 20, 2015

#‎አላህ_ይጠብቃት‬



#‎አላህ_ይጠብቃት‬

በፀዳችው ሀገር በሱዑዲ ሜዳ
በነብዩ ምድር በቅዱሷ ጓዳ
ተውሒድ ተንሰራፍቶ ሽርኩ ሲሽመደመድ
ሱና ምደሩን ሞልቶት ቢድዓ ሲቆራመድ
ያየ በሽተኛ የታወረ ቀልቡ
ከኢብሊስ ጋር ዘምቶ የከረፋ ልቡ
ሌት ተቀን ይተጋል ስም እያጎደፈ
በተውሒድ አገር ላይ ዋሽቶ እየቀጠፈ።
አላህ ይጠብቃት ሱዑዲን ከሴረኛ
ከኢራን ሙሽሪኮች ከኢኽዋን መጋኛ
ከ"ዴሞክራሲ" ዛር ከምዕራብ ቅጥረኛ።
 
 

የውጫጭ ጥርቅም



የውጫጭ ጥርቅም

የዛ ጀግና ብዕር የሸኽ ረቢዕ ምላሽ
የሱፍያን በሽታ በ”ረዶቹ” አስታጋሽ
የኢኽዋንን ቅጥፈት በሱና አፈራራሽ
በቢድዓ አጨብጫቢ ውሸታም ጉሮሮ
የሸኽ ረቢዕ ትችት ውስጡ ተሰንቅሮ 
እንደ ብርቱው እሾህ ገብቶ ተቀርቅሮ
አላስቆም አላስኬድ ብሎት አስቸግሮ
በቁርአን በሓዲስ ቢይዘው ወጥሮ
በርታ ቀጥል አለው የዘመን ዑለማ
ኢብኑ ባዝ አልባኒ ሌላ እሱን የሰማ
ሙቅቢልም ወደደው ፈውዛን አወደሰው
ዑሰይሚን ተው አለ የዘለፈውን ሰው
በኒህ ከዋክብቶች በኡማው ጨረቃ
መልካም ተብሎለት ተሹሞ ሲያበቃ
ውጫጩ ቢንጫጫ ያቅሙን ድንበር ሰብሮ
ኢኽዋኑ ከተክፊር አንድ ላይ አብሮ
ረቢዕ ላይ ቢዘምትም ሓዳዲን ጨምሮ 
ምን ይጎዳል አቦ! የመንደር ጫጫታ
የውጫጭ ጥርቅም የጃሂል እሪታ!


Friday, October 2, 2015

የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ - ክፍል 6



ለእስልምና ማእዘናት ማስረጃችን

ከሓዲስ

أنْ تُؤْمِنَ بِاَللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ، وَتُؤْمِنَ بِالْقَدَرِ خَيْرِهِ وَشَرِّهِ.


َرَوَاهُ مُسْلِمٌ

ነብዩ ሙሀመድ(ሰለላ ዐለይሂ ወሰላም)በሶሒሕ ሐዲስ እንዲህ ብለዋል ፦ “ እምነት(ኢማን)ማለት በአላህ ማመን፣ በመፃሀፋት ማመን፣ በመልእክተኞች ማመን፣ በመጨረሻው ቀን ማመን፣ በቀደር(በአላህ ውሳኔ) በጀም ከፋም ማመን ነው።

ሓዲሱን ሙስሊም ዘግቦታል።