Thursday, February 26, 2015

የእስልምና ዓቂዳ(የእስልምና መሰረቶች) ትምህርት ከኢርሻድ ኪታብ። 3



የእስልምናን ዓቂዳ ለራሳችን ከተማርን እና ካወቅን ቡሃላ ተግባራዊ ማድረግ አለብን። ተግባራዊ ያልሆነ ማወቅ እወቀት አይባልም። ቀጥሎ የሚመጣው ደረጃ ደግሞ ሰዎችን ወደዚህ ንጹህ እምነት መጥራት ነው። ለራሳችን አውቀናል ወይንም ሰርተናል ብሎ ሰው እየጠመመና እየተሳሳተ ዝም ብሎ ማየት በእስልምና የተወገዘ ተግባር ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን የዚህ እውቀትና ተግባር ባለቤት የሆነውም ዝም በማለቱ እሱ ራሱ ሊጠምም ይችላል።

1. ስለዚህ ባጠቃላይ የእስልምናን ዓቂዳ(የእስልምናን መሰረት)
2. መማር(ማወቅ)፥
3. ተግባራዊ ማድረግ፥
4. ሰዎችን ማስተማር(ጥሪ ማድረግ)፥



እነዚህን 3ት ነገሮችን ስንሰራ ለሚደርስብን ችግር ትዕግስት ማድረግ፥ ግዴታ ነው።

No comments:

Post a Comment