እኚህ ናቸው ሰለፎቼ (5)
በ ወንድም Ibnu Munewer
ሁለት የቢድዐ ተከታዮች ሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን ዘንድ ገቡና
"የበክር አባት ሆይ የሆነ ሐዲሥ እናውራህ?" አሉት።
"አይሆንም " አለ።
"ከአላህ ኪታብ የሆነች አንቀፅ እናንብብልህ?" አሉ።
"አይሆንም። ትወጡልኛላችሁ ያለበለዚያ እኔ እወጣላችኋለሁ" አላቸው።
በቦታው የነበሩ የተወሰኑ ሰዎች "የበክር አባት ሆይ! ምን ነበር ከአላህ ኪታብ (ከቁርኣን) አንቀፅ ቢያነቡልህ ምን ችግር ነበረው?” አሉት፡፡
ይህኔ ሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን እንዲህ አለ፡- “እኔ የሆነች የቁርኣን አንቀፅን ቀርተው አዛብተው እንዳያቀርቧት ከዚያም ያ ያዛቡት ነገር ልቤ ላይ እንዳይቀር ሰግቼ ነው” አለ፡፡ [አስሱናህ፣ ዐብዱላህ ኢብኒልኢማም አሕመድ፡ 1/138]
ይህን ከታላቅ ሰው የወጣ ታላቅ ትውፊት በሚገባ ያጢኑት፡፡ በሚገባም ይስሩበት፡፡ የህይወት መመሪያም ያድርጉት፡፡ ጆሮዎትን ለሙብተዲዕ አያመቻቹ፡፡ “ጥሩ ጥሩን እወስዳለሁ፣ መጥፎ መጥፎውን እተዋለሁ” እያሉ አይፈላሰፉ፡፡ ጥሩ እና መጥፎ ከለየህ እድለኛ ነህ ጎሽ! ባይሆን ሙብተዲዕ ከምታዳምጥ ቁጭ ብለህ አስተምር፡፡ አዋ!! ሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን ታላቅ ታቢዒይ ነው፣ ሁሉ የሚመሰክርለት ታላቅ ዐሊም፡፡ ግና ከቢድዐ አደጋ በእውቀቱ አልተማመነም፡፡ ታዲያ እኛ የምንተማመነው በምናችን ነው?! ነው ወይስ እውቀታችን ከሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን በላይ ነው? ይልቅ እራስህን ጠብቅ፡፡ “ሹቡሃት ሲበዛ ጠላፊዎች ናቸው!! ልቦች ደግሞ ደካሞች ናቸው” ይላሉ፡፡ የቢድዐን አደጋ እና የልብን ደካማነት የሚያውቁት ጠቢባን፡፡ በቢድዐ ቫይረስ የተበከሉ ግብዞች ግን ጆሯቸውን ለሙብተዲዖች ይጥላሉ፤ ከሙብተዲዕ ስር ሊቀሩ ይንበረከካሉ፤ የሙብተዲዖችን ድስኩር ለመስማት መጅሊስ ያጨናንቃሉ፡፡ የሙብተዲዖችን መርዛማ ኪታቦች በገዛ ገንዘባቸው ይገዛሉ፡፡ “ምነው?” ሲባሉ ችግሩን አውቃለሁ፡፡ እየመረጥኩ እወስዳለሁ ብየ ነው” ይላሉ፡፡ ዐጂብ ፍልስፍና!! ዐጂብ የሆነ በራስ መኮፈስ፡፡ ብዙም ሳይቆዩ ዋጋቸውን ያገኛሉ፡፡ ለሱና ያላቸውን ፍቅር፣ ለቢድዐ ያላቸውን ጥላቻ ዐቂደቱልወላእ ወልበራእን በራሳቸው ሳንቲም ከልባቸው ውስጥ ይረሽናሉ፡፡ ከዚያም ይህን ቅጥ ያጣ “ስፋታቸውን” መንቃት፣ አርቆ ማሰብ ያደርጉታል፡፡
ይህን ለመፃፍ ያነሳሳኝ በቅርቡ በታላቁ ሐበሻዊ ዐሊም ሙሐመድ አማን አልጃሚ ረሒመሁላህ ላይ የተቀጠፉ አስቀያሚ ውንጀላዎችን ማየቴ ነው፡፡ ሙሐመድ አማንን የመንግስት ቅጥረኛ እንደነበሩ፣ ዑለማዎችን አሳልፈው ይሰጡ የነበሩ ሰላይ እንደነበሩ፣ ወዘተ በሚያስጠሉ ቃላት ሲወርፉ ማየት ምንኛ የሚያሳዝን ነገር ነው? በርግጥ ከቢድዐ ሰዎች ከዚህ የተሻለ መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡ የቢድዐ ሰዎች ዑለማን ስለማክበር የሚደሰኩሩት ካንገት በላይ እንደሆነ ያሳየ ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ “ዑለማን እናክብር” ሲሉ የሚፈልጉት የቢድዐ ቁንጮዎቻቸውን እንድናንቆለጳጵስ እንጂ የሱና ዑለማዎችንማ ይሄው በሌሉበት በሀሰት እየወነጀሏቸው ነው፡፡ አላማቸው ወጣቱን ከሱና ዑለማ ማራቅ ነው፣ ከዚያም ጭፍን የነሱ ተከታይ ማድረግ፡፡ ዐረብ የሆኑ ኢኽዋኖች ሸይኽ ሙሐመድ አማን አልጃሚን የትኛውንም ሰለፊ ከሚወርፉት በላይ ይወርፏቸዋል፣ አዲስ አንጃ እንደመሰረቱም ይቀጥፉባቸዋል፡፡ ከማንም በላይ እሳቸው ላይ ያነጣጠሩት ዐረብ ስላልሆኑ ነው፡፡ ሸይኽ አልጃሚ ምንም እንኳን በታላላቅ የሱና ዑለማዎች እጅግ የሚገርም አድናቆትን ቢቸሩም ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ስማቸውንም የሚያውቀው ጥቂት ነው፡፡ ስንቱ የሱፍያ ሸይኾች ድንበር ባለፈ መልኩ በሚሞካሹበት ምድር የሳቸው ግን ታሪካቸውም አይወራም፡፡ ምክንያቱ ግልፅ ነው፡፡ ሸይኹ ሲበዛ ሱናህ ላይ ብርቱ ነበሩ ረሒመሁላህ፡፡ ሸይኹ የታላላቅ የሱና ዑለማዎች ሸይኽ ናቸው፡፡ ተማሪዎቻቸው እንኳን በአለም አቀፍ ደረጃ የሚያበሩ ደማቅ ከዋክብት ናቸው፡፡
እዚህ ግባ የማይባሉ የሰፈር ሸይኾችን ሳይቀር “ከነ ሸይኽ ፈውዛን በምን ያንሳሉ? ሃበሻ ስለሆኑ ነው እንዴ?” እያሉ ስውር በሆነ መልኩ ሌሎች የሱና ዑለማዎችን በዘረኝነት እየወረፉ የቢድዐ ድሪቶዎቻቸውን ለመቆለል የሚጣጣሩ ሰዎች ይሄን “ለወንዝ ሰው” መቆርቆራቸውን ግን ለሸይኽ ሙሐመድ አማን አልጃሚ ሲሆን አይተገብሩትም፡፡
የቢድዐ አጫፋሪዎች በጭፍን የሳዑዲ ዑለማዎችን እንደምንከተል ያስተጋባሉ፡፡ ይሄ አይን ያወጣ ቅጥፈት ነው፡፡ መለኪያችን አካሄዳቸው እንጂ ዜግነታቸው አይደለም፡፡ አዎ እንደነሱ “የሀገር ውስጥ” እና “የባህር ማዶ” በሚል ዑለማዎችን ለሁለት አንከፍልም፡፡ አዎ ታላላቅ የሱና ዑለማዎችን “የሀገራችን” አይደሉም በሚል ትምህርቶቻቸውን ገሸሽ አናደርግም፡፡ ይሄ የቦዘኔ እስፖርተኞች አካሄድ እንጂ የዲን አካሄድ አይደለምና፡፡ ይሄኮ በጭፍን ቲፎዞ የሚኮንበት ኳስ ወይም ሩጫ አይደለም፡፡ ስለዚህ የውጭም ቢሆኑ ሱኒዎችን እንወዳለን፡፡ የውስጥም ቢሆኑ ሙብተዲዖችን እንጠላለን፡፡ እነ ሸይኽ ኢብኑ ባዝ፣ ኢብኑ ዑሠይሚን፣ ፈውዛን፣ ረቢዕ፣ አልሉሐይዳን፣ አልዐባድ፣ ዑበይድ፣… የወደድናቸው ሳኡዲያውያን ስለሆኑ ሳይሆን ጠንካራ የሱና ሰዎች ስለሆኑ ነው፡፡ እንጂማ እነ ሰልማን አልዐወዳህ፣ ሰፈር ሐዋሊ፣ ዓይዱልቀርኒ፣ ዐሪፊን እና መሰሎቻቸውን ሳዑዲያውያን መሆናቸው እንድንወዳቸው አያደርገንም፡፡ የቢድዐ አካሄዳቸው እንድንጠላቸው ያስገድደናልና፡፡ እነ ሐሰን አልበና፣ ሰይድ ቁጥብ፣ ቀርዷዊ፣ … ወዘተ የምንጠላቸው የቢድዐ ቁንጮዎች ስለሆኑ እንጂ ግብፃውያን ስለሆኑ አይደለም፡፡ በጭራሽ!! እንጂማ እዚያው ግብፅ ውስጥ እነ ሙሐመድ ሰዒድ ረስላንን፣ እነ ሐሰን ዐብዱልወሃብ አልበናን፣ እነ ጦልዐት ዘህራንን፣... እንወዳለን፡፡ ከሌላውም አለም እነ አልባኒን፣ ሙቅቢልን፣ ሙሐመድ አሚን አሽሺንቂጢን፣ እነ ዑመር ፈላታን፣ እነ ሙሐመድ ዐብዱልወሃብ አልወሷቢን፣ እነ ሙሐመድ ዐሊ ፈርኩስን፣ … የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ቢሆኑም እንወዳለን፡፡ የወደድናቸው የውጭ የማድነቅ አባዜ ኖሮብን ሳይሆን የተከተሉት መንገድ አንድነት ነው፡፡ የሀገሬን አልጠላም፡፡ ለምንስ ሲባል እጠላለሁ?! እሄው የሀረሩን ጀግና ሸይኽ ሙሐመድ አማን አልጃሚን እና መሰሎቻቸውን እጅግ በጣም እወዳቸዋለሁ፡፡ የወደድኳቸው ግን ኢትዮጵያዊ ስለሆኑ አይደለም፣ ብርቱ የሱናህ ሰው ስለነበሩ እንጂ፣ ረሒመሁላህ፡፡ መስመራቸውን የቢድዐ መስመር ያደረጉትን በሙሉ ዜግነታቸውን ከግምት ሳላስገባ አልወዳቸውም፡፡
እዚጋ “ሁሉስ ሙስሊሞች አይደሉ? ምንድን ነው እየመረጡ መውደድ?” የሚል ይኖር ይሆናል፣ ጊዜው ዐጃዒብ የበዛበት ነውና፡፡ በዚህ ረገድ የተነገሩ ጥቂት የቀደምቶቻችንን ትውፊቶች በመጥቀስ ፅሁፌን ልዝጋ
1. “እኔ ከአህሉ ሱንናህ የሆነ ሰው መሞቱ ሲነገረኝ ልክ ከአካል ክፍሎቼ የተወሰነውን ያጣው ያክል እሆናለሁ!!” አዩብ አስሰኽቲያኒ ረሒመሁላህ፡፡
2. “በምስራቅ ስለሚገኝ አንድ የሱና ሰው፣ እንዲሁም በምእራብ ስለሚገኝ ሌላ የሱና ሰው ከሰማህ ሰላምታ ላክላቸው፡፡ ዱዐም አድርግላቸው፡፡ የሱና እና የጀማዓ ሰዎች ምንኛ ጥቂቶች ናቸው?!!” ሱፍያን አሥሠውሪ ረሒመሁላህ፡፡
3. አሰድ ኢብኑ ሙሳ እንዲህ ይላል፡- “ሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህ ዘንድ ነበርን፡፡ የደራወርዲ መርዶ ደረሰው፡፡ (በስህተት ነው እንጂ ሰውየው አልሞተም ነበር፡፡) እጅግ አዘነ፡፡ ቁጭቱንም ግልፅ አወጣው፡፡ ‘ይህን ያክል የምትደርስ አይመስለንም ነበር’ አልነው፡፡ ‘ከአህሉ ሱናህ እኮ ነው!!’” አለ፡፡
4. “ከነችግራቸው የሱናህ ሰዎችን ውደዱ፡፡ እኛንም እናንተንም አላህ በሱናህ እና በጀማዐህ ላይ ይግደለን፡፡” አልኢማም አሕመድ ረሒመሁላህ፡፡
ማሳሰቢያ!
የቢድዐ ሰዎችን እንጠላለን ማለት በጥፋታቸው ልክ እንጂ ከሃዲዎችን የምንጠላውን ያክል ነው ማለት አይደለም፡፡ ወሰላም፡፡
(ኢብኑ ሙነወር፡ ግንቦት 01/2007)
በ ወንድም Ibnu Munewer
በ ወንድም Ibnu Munewer
ሁለት የቢድዐ ተከታዮች ሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን ዘንድ ገቡና
"የበክር አባት ሆይ የሆነ ሐዲሥ እናውራህ?" አሉት።
"አይሆንም " አለ።
"ከአላህ ኪታብ የሆነች አንቀፅ እናንብብልህ?" አሉ።
"አይሆንም። ትወጡልኛላችሁ ያለበለዚያ እኔ እወጣላችኋለሁ" አላቸው።
በቦታው የነበሩ የተወሰኑ ሰዎች "የበክር አባት ሆይ! ምን ነበር ከአላህ ኪታብ (ከቁርኣን) አንቀፅ ቢያነቡልህ ምን ችግር ነበረው?” አሉት፡፡
ይህኔ ሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን እንዲህ አለ፡- “እኔ የሆነች የቁርኣን አንቀፅን ቀርተው አዛብተው እንዳያቀርቧት ከዚያም ያ ያዛቡት ነገር ልቤ ላይ እንዳይቀር ሰግቼ ነው” አለ፡፡ [አስሱናህ፣ ዐብዱላህ ኢብኒልኢማም አሕመድ፡ 1/138]
ይህን ከታላቅ ሰው የወጣ ታላቅ ትውፊት በሚገባ ያጢኑት፡፡ በሚገባም ይስሩበት፡፡ የህይወት መመሪያም ያድርጉት፡፡ ጆሮዎትን ለሙብተዲዕ አያመቻቹ፡፡ “ጥሩ ጥሩን እወስዳለሁ፣ መጥፎ መጥፎውን እተዋለሁ” እያሉ አይፈላሰፉ፡፡ ጥሩ እና መጥፎ ከለየህ እድለኛ ነህ ጎሽ! ባይሆን ሙብተዲዕ ከምታዳምጥ ቁጭ ብለህ አስተምር፡፡ አዋ!! ሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን ታላቅ ታቢዒይ ነው፣ ሁሉ የሚመሰክርለት ታላቅ ዐሊም፡፡ ግና ከቢድዐ አደጋ በእውቀቱ አልተማመነም፡፡ ታዲያ እኛ የምንተማመነው በምናችን ነው?! ነው ወይስ እውቀታችን ከሙሐመድ ኢብኑ ሲሪን በላይ ነው? ይልቅ እራስህን ጠብቅ፡፡ “ሹቡሃት ሲበዛ ጠላፊዎች ናቸው!! ልቦች ደግሞ ደካሞች ናቸው” ይላሉ፡፡ የቢድዐን አደጋ እና የልብን ደካማነት የሚያውቁት ጠቢባን፡፡ በቢድዐ ቫይረስ የተበከሉ ግብዞች ግን ጆሯቸውን ለሙብተዲዖች ይጥላሉ፤ ከሙብተዲዕ ስር ሊቀሩ ይንበረከካሉ፤ የሙብተዲዖችን ድስኩር ለመስማት መጅሊስ ያጨናንቃሉ፡፡ የሙብተዲዖችን መርዛማ ኪታቦች በገዛ ገንዘባቸው ይገዛሉ፡፡ “ምነው?” ሲባሉ ችግሩን አውቃለሁ፡፡ እየመረጥኩ እወስዳለሁ ብየ ነው” ይላሉ፡፡ ዐጂብ ፍልስፍና!! ዐጂብ የሆነ በራስ መኮፈስ፡፡ ብዙም ሳይቆዩ ዋጋቸውን ያገኛሉ፡፡ ለሱና ያላቸውን ፍቅር፣ ለቢድዐ ያላቸውን ጥላቻ ዐቂደቱልወላእ ወልበራእን በራሳቸው ሳንቲም ከልባቸው ውስጥ ይረሽናሉ፡፡ ከዚያም ይህን ቅጥ ያጣ “ስፋታቸውን” መንቃት፣ አርቆ ማሰብ ያደርጉታል፡፡
ይህን ለመፃፍ ያነሳሳኝ በቅርቡ በታላቁ ሐበሻዊ ዐሊም ሙሐመድ አማን አልጃሚ ረሒመሁላህ ላይ የተቀጠፉ አስቀያሚ ውንጀላዎችን ማየቴ ነው፡፡ ሙሐመድ አማንን የመንግስት ቅጥረኛ እንደነበሩ፣ ዑለማዎችን አሳልፈው ይሰጡ የነበሩ ሰላይ እንደነበሩ፣ ወዘተ በሚያስጠሉ ቃላት ሲወርፉ ማየት ምንኛ የሚያሳዝን ነገር ነው? በርግጥ ከቢድዐ ሰዎች ከዚህ የተሻለ መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡ የቢድዐ ሰዎች ዑለማን ስለማክበር የሚደሰኩሩት ካንገት በላይ እንደሆነ ያሳየ ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ “ዑለማን እናክብር” ሲሉ የሚፈልጉት የቢድዐ ቁንጮዎቻቸውን እንድናንቆለጳጵስ እንጂ የሱና ዑለማዎችንማ ይሄው በሌሉበት በሀሰት እየወነጀሏቸው ነው፡፡ አላማቸው ወጣቱን ከሱና ዑለማ ማራቅ ነው፣ ከዚያም ጭፍን የነሱ ተከታይ ማድረግ፡፡ ዐረብ የሆኑ ኢኽዋኖች ሸይኽ ሙሐመድ አማን አልጃሚን የትኛውንም ሰለፊ ከሚወርፉት በላይ ይወርፏቸዋል፣ አዲስ አንጃ እንደመሰረቱም ይቀጥፉባቸዋል፡፡ ከማንም በላይ እሳቸው ላይ ያነጣጠሩት ዐረብ ስላልሆኑ ነው፡፡ ሸይኽ አልጃሚ ምንም እንኳን በታላላቅ የሱና ዑለማዎች እጅግ የሚገርም አድናቆትን ቢቸሩም ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ስማቸውንም የሚያውቀው ጥቂት ነው፡፡ ስንቱ የሱፍያ ሸይኾች ድንበር ባለፈ መልኩ በሚሞካሹበት ምድር የሳቸው ግን ታሪካቸውም አይወራም፡፡ ምክንያቱ ግልፅ ነው፡፡ ሸይኹ ሲበዛ ሱናህ ላይ ብርቱ ነበሩ ረሒመሁላህ፡፡ ሸይኹ የታላላቅ የሱና ዑለማዎች ሸይኽ ናቸው፡፡ ተማሪዎቻቸው እንኳን በአለም አቀፍ ደረጃ የሚያበሩ ደማቅ ከዋክብት ናቸው፡፡
እዚህ ግባ የማይባሉ የሰፈር ሸይኾችን ሳይቀር “ከነ ሸይኽ ፈውዛን በምን ያንሳሉ? ሃበሻ ስለሆኑ ነው እንዴ?” እያሉ ስውር በሆነ መልኩ ሌሎች የሱና ዑለማዎችን በዘረኝነት እየወረፉ የቢድዐ ድሪቶዎቻቸውን ለመቆለል የሚጣጣሩ ሰዎች ይሄን “ለወንዝ ሰው” መቆርቆራቸውን ግን ለሸይኽ ሙሐመድ አማን አልጃሚ ሲሆን አይተገብሩትም፡፡
የቢድዐ አጫፋሪዎች በጭፍን የሳዑዲ ዑለማዎችን እንደምንከተል ያስተጋባሉ፡፡ ይሄ አይን ያወጣ ቅጥፈት ነው፡፡ መለኪያችን አካሄዳቸው እንጂ ዜግነታቸው አይደለም፡፡ አዎ እንደነሱ “የሀገር ውስጥ” እና “የባህር ማዶ” በሚል ዑለማዎችን ለሁለት አንከፍልም፡፡ አዎ ታላላቅ የሱና ዑለማዎችን “የሀገራችን” አይደሉም በሚል ትምህርቶቻቸውን ገሸሽ አናደርግም፡፡ ይሄ የቦዘኔ እስፖርተኞች አካሄድ እንጂ የዲን አካሄድ አይደለምና፡፡ ይሄኮ በጭፍን ቲፎዞ የሚኮንበት ኳስ ወይም ሩጫ አይደለም፡፡ ስለዚህ የውጭም ቢሆኑ ሱኒዎችን እንወዳለን፡፡ የውስጥም ቢሆኑ ሙብተዲዖችን እንጠላለን፡፡ እነ ሸይኽ ኢብኑ ባዝ፣ ኢብኑ ዑሠይሚን፣ ፈውዛን፣ ረቢዕ፣ አልሉሐይዳን፣ አልዐባድ፣ ዑበይድ፣… የወደድናቸው ሳኡዲያውያን ስለሆኑ ሳይሆን ጠንካራ የሱና ሰዎች ስለሆኑ ነው፡፡ እንጂማ እነ ሰልማን አልዐወዳህ፣ ሰፈር ሐዋሊ፣ ዓይዱልቀርኒ፣ ዐሪፊን እና መሰሎቻቸውን ሳዑዲያውያን መሆናቸው እንድንወዳቸው አያደርገንም፡፡ የቢድዐ አካሄዳቸው እንድንጠላቸው ያስገድደናልና፡፡ እነ ሐሰን አልበና፣ ሰይድ ቁጥብ፣ ቀርዷዊ፣ … ወዘተ የምንጠላቸው የቢድዐ ቁንጮዎች ስለሆኑ እንጂ ግብፃውያን ስለሆኑ አይደለም፡፡ በጭራሽ!! እንጂማ እዚያው ግብፅ ውስጥ እነ ሙሐመድ ሰዒድ ረስላንን፣ እነ ሐሰን ዐብዱልወሃብ አልበናን፣ እነ ጦልዐት ዘህራንን፣... እንወዳለን፡፡ ከሌላውም አለም እነ አልባኒን፣ ሙቅቢልን፣ ሙሐመድ አሚን አሽሺንቂጢን፣ እነ ዑመር ፈላታን፣ እነ ሙሐመድ ዐብዱልወሃብ አልወሷቢን፣ እነ ሙሐመድ ዐሊ ፈርኩስን፣ … የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ቢሆኑም እንወዳለን፡፡ የወደድናቸው የውጭ የማድነቅ አባዜ ኖሮብን ሳይሆን የተከተሉት መንገድ አንድነት ነው፡፡ የሀገሬን አልጠላም፡፡ ለምንስ ሲባል እጠላለሁ?! እሄው የሀረሩን ጀግና ሸይኽ ሙሐመድ አማን አልጃሚን እና መሰሎቻቸውን እጅግ በጣም እወዳቸዋለሁ፡፡ የወደድኳቸው ግን ኢትዮጵያዊ ስለሆኑ አይደለም፣ ብርቱ የሱናህ ሰው ስለነበሩ እንጂ፣ ረሒመሁላህ፡፡ መስመራቸውን የቢድዐ መስመር ያደረጉትን በሙሉ ዜግነታቸውን ከግምት ሳላስገባ አልወዳቸውም፡፡
እዚጋ “ሁሉስ ሙስሊሞች አይደሉ? ምንድን ነው እየመረጡ መውደድ?” የሚል ይኖር ይሆናል፣ ጊዜው ዐጃዒብ የበዛበት ነውና፡፡ በዚህ ረገድ የተነገሩ ጥቂት የቀደምቶቻችንን ትውፊቶች በመጥቀስ ፅሁፌን ልዝጋ
1. “እኔ ከአህሉ ሱንናህ የሆነ ሰው መሞቱ ሲነገረኝ ልክ ከአካል ክፍሎቼ የተወሰነውን ያጣው ያክል እሆናለሁ!!” አዩብ አስሰኽቲያኒ ረሒመሁላህ፡፡
2. “በምስራቅ ስለሚገኝ አንድ የሱና ሰው፣ እንዲሁም በምእራብ ስለሚገኝ ሌላ የሱና ሰው ከሰማህ ሰላምታ ላክላቸው፡፡ ዱዐም አድርግላቸው፡፡ የሱና እና የጀማዓ ሰዎች ምንኛ ጥቂቶች ናቸው?!!” ሱፍያን አሥሠውሪ ረሒመሁላህ፡፡
3. አሰድ ኢብኑ ሙሳ እንዲህ ይላል፡- “ሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህ ዘንድ ነበርን፡፡ የደራወርዲ መርዶ ደረሰው፡፡ (በስህተት ነው እንጂ ሰውየው አልሞተም ነበር፡፡) እጅግ አዘነ፡፡ ቁጭቱንም ግልፅ አወጣው፡፡ ‘ይህን ያክል የምትደርስ አይመስለንም ነበር’ አልነው፡፡ ‘ከአህሉ ሱናህ እኮ ነው!!’” አለ፡፡
4. “ከነችግራቸው የሱናህ ሰዎችን ውደዱ፡፡ እኛንም እናንተንም አላህ በሱናህ እና በጀማዐህ ላይ ይግደለን፡፡” አልኢማም አሕመድ ረሒመሁላህ፡፡
ማሳሰቢያ!
የቢድዐ ሰዎችን እንጠላለን ማለት በጥፋታቸው ልክ እንጂ ከሃዲዎችን የምንጠላውን ያክል ነው ማለት አይደለም፡፡ ወሰላም፡፡
(ኢብኑ ሙነወር፡ ግንቦት 01/2007)
በ ወንድም Ibnu Munewer

No comments:
Post a Comment